Friday, March 8, 2013

ስትሠራ እንጂ ስታስብ መሳሳት የለብህም


“የማይሠራ ሰው አይሳሳትም” የሚለው አባባል የሰው ልጅ በስራ ላይ ሳለ ስህተት ቢፈጽም እንኳ ሰብዓዊ ባህርይ ነውና ከስህተቱ እንዲማር መምከር እንደሚገባ እንጂ በአግራሞት የሚታይ ጉዳይ እንዳልሆነ የሚያስተምር ነው፡፡ ነገር ግን በስራው ላይ የተፈጠረው ስህተት ከተግባር ሳይሆን ከተሳሳተ አስተሳሰብ የመነጨ ከሆነ ነገሩ የከፋ ይሆናል፤ ምክንያቱም   በአስተሳሰቡ ላይ ህጸጽ ያለበት ሰው የሚሰራው ወይም የሚናገረው ሁሉ ስህተት ስለሆነና ለእርሱ ለባለቤቱ ግን ስህተቱ ሁሉ ትክክል ስለሚመስለው በቀላሉ እውነት ላይ ለመድረስ ወይም ትክክለኛ ስራ ለመስራት እጅግ በጣም ከባድ ይሆንበታልና፡፡   
የሚናገሩና የሚጽፉ ሰዎች ስለትክክለኛ አስተሳሰብ ምንነት ባለማወቅ ወይም እያወቁ ሌሎችን ለማታለል በማሰብ የአስተሳሰብን ህጸጾችን (ፋላሲ) ሊፈጽሙ ይችላሉ፡፡ እነዚህ ህጸጾች በቅዱሳት መጻህፍት አረዳድና አተናተን፣ በቴሌቪዥንና ሬዲዮ የማስታወቂያ ቋንቋ፣ በጥናትና ምርምር ስራዎች፣በፖሊስ ምርመራና በፍርድ ቤት ችሎት ሂደት፣ በታላላቅ ስብሰባዎችና ክርክር መድረኮች፣ በአሰሪና ሰራተኛ የስራ ምልልስ እንዲሁም በግለሰቦች የዕለት ተዕለት ተግባቦታዊ ምልልስና በመሳሰሉት ማናቸውም የህይወት መድረኮች ላይ ሊፈጸሙ ይችላሉ፡፡
አሪስጣጣሊስና ከእርሱ በኋላ የተነሱ የትክክለኛ አስተሳሰብ ጠበብት የአስተሳሰብ ህጸጾችን በተለያዩ ፈርጆች ከፋፍለው አቅርበዋል፡፡ የዚህ ጹሁፍ ዋና ዓላማም አንባብያን የአስተሳሰብ ህጸጾችን ምንነት፣ እንዲሁም የሚፈጸሙበትን ምክንያት በዝርዝር በማጥናት የተሳሳተ ውሳኔ ከመስጠት ራሳቸውን እንዲቆጥቡና በሌሎች ከተሳሳተ አስተሳሰብ የመነጨ ንግግርና ጽሁፍ  እንዳይታለሉ  መታደግ ነው፡፡         
የመጀመሪው የአስተሳሰብ ህጸጽ ከዕውቀት ማነስ (ignorance) የሚመነጭ ነው፡፡ ለምሳሌ አንድ ሰው “ስለ መላዕክት ህልውና በእርግጠኝነት የሚታወቅ ነገር የለም፡፡” ከሚል አንድ ማስረጃ ላይ ተነስቶ “በዓለም ላይ መላዕክት የሚባሉ ነገሮች የሉም” የሚል ድምዳሜ ላይ ቢደርስ ስህተት ላይ ይወድቃል፤ ምክንያቱም አንድን ድምዳሜ ለመስጠት አለማወቅን እንደ አመክንዮ መጠቀም የአስተሳሰብ ህጸጽ ከመሆኑም ባሻገር ትክክለኛው የአስተሳሰብ መርህ ነገሩን አስከምናውቀው ድረስ ድምዳሜ ከመስጠት መቆጠብን ያስተምራልና፡፡
ሁለተኛው የአስተሳሰብ ህጸጽ አካላዊ ወይም ስነልቦናዊ ኃይልን በመጠቀም ወይም በማስፈራራት ለማሳመን በሚደረግ ሙከራ የሚፈጠር ስህተት ነው፡፡ ለምሳሌ አንድ መርማሪ ፖሊስ ተጠርጣሪውን ግለሰብ ፈጸመ ስለተባለው ወንጀል ለማሳመን ልዩ ልዩ የድምጽ፣ የምስልና የሰው ማስረጃዎችን በማቅረብ ፈንታ ተጠርጣሪው ላይ አካላዊ ጥቃት (ድብደባ) በማድረስ ወይም በማስፈራራት ግለሰቡ ያልሰራውን ሰርቻለሁ፣ ያልፈጸመውን ፈጽሜያለሁ ብሎ የእምነት ቃሉን እንዲሰጥ በማስገደድ አሳምኖት ተጠርጣሪው ወንጀሉን እንደፈጸመ አምኗል የሚል ድምዳሜ ላይ ቢደርስ በትክክለኛ አስተሳሰብ መርህ መሰረት ኃይልን መጠቀም (Appeal to Force) የተባለውን የአስተሳሰብ ህጸጽ ፈጽሟል ማለት ነው፡፡
በአድማጭ ወይም በአንባቢው ልብ ውስጥ የሐዘን ስሜትን በመጫር (Appeal to Pity) ለማሳመን የሚደረግ ሙከራ ሶስተኛው የአስተሳሰብ ህጸጽ መገለጫ ነው፡፡ አንድ ተማሪ በግል ኑሮው ላይ የገጠመውን ችግር እንባ በተቀላቀለበት ሁኔታ ዘርዝሮ ለመምህሩ በማስረዳት ምንም እንኳን የትምህርቱን ይዘት በሚፈለገው ደረጃ ባያውቀውም መምህሩ እንዲያዝንለትና ጥሩ ውጤት እንዲመዘግብለት አስተዛዝኖ ቢለምንና ቢሳካለት ተማሪው መምህሩን የአስተሳሰብ ህጸጽ ውስጥ ዘፍቆታል ማለት ነው፡፡          
በከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ውስጥ በተደጋጋሚ የሚከሰቱ አብዛኞቹ የተማሪዎች የብሄር ግጭቶች የብዙሃኑን ስሜት በጅምላ ማነሳሳት (Mob mentality) በሚባል ለሚታወቀው የአስተሳሰብ ህጸጽ በአብነት የሚቀርቡ ናቸው፡፡ ትክክለኛ አስተሳሰብ ከስሜታዊነትና ከቡድን መንፈስ የጸዳ፤ በአመክንዮና በተረጋጋ ግላዊ ተመስጦ የሚደረስበት መንገድ ነው፡፡ ሰዎች የበለጠ ስሜታውን እየሆኑ በመጡ ቁጥር ይበልጡኑ ከአመክንዮ እየራቁ ይመጣሉ፤ ይበልጡኑ ከአመክንዮ በራቁ ቁጥር ይበልጡኑ የአስተሳሰብ ህጸጽ ውስጥ ይዘፈቃሉ፡፡ ለዚህም ነው የተለያየ ብሄረሰብ አባላት በሆኑ ሁለት ግለሰብ ተማሪዎች መካከል የተፈጠረን ተራ ዕለታዊ ግጭት “የብሄራችን ልጅ ተነካ!” በሚል የቡድን (mob) ስሜት ተነሳስተው በማይመለከታቸው ጉዳይ በርካታ ተማሪዎች አላስፈላጊ የብሄር ግጭት ውስጥ ሲገቡና ራሳቸውን ችግር ላይ ሲጥሉ የምንመለከተው፡፡
በማስታወቂያ ቋንቋ ውስጥ የሚገኙት አብዛኞቹ የአስተሳሰብ ህጸጾች አንድ ግለሰብ ራሱን ከብዙሃኑ ጋር በማነጻጸር የበታችነት ወይም የበላይነት ስሜት እንዲፈጠርበት በማድረግ እንዲሁም ታዋቂ ግለሰቦችን ከአንድ ምርት ወይም አገልግሎት ጋር በማቆራኘት የሚፈጠሩ ናቸው፡፡ የመጀመሪያውና (Bandwagon Argument) በመባል የሚታወቀው የአስተሳሰብ ህጸጽ ግለሰቡ ራሱን ከብዙሃኑ ጋር በማነጻጸር የበታችነት ስሜት እንዲሰማውና ከዚህ አሉታዊ ስሜትም ለመውጣት ሲል ብቻ ተገቢ ምክንያት ሳያገኝ በማሳመኛው መደምደሚያ ላይ የቀረበውን ዓረፍተ ነገር እውነትነት እንዲቀበል የሚገደድበት መንገድ ነው፡፡ ለምሳሌ አንድ የፊልም ማስታወቂያ “በድፍን አዲስ አበባ መነጋገሪያ የሆነ ድንቅ ፊልም…” ወይም አንድ የቢራ ካምፓኒ “በመላ ሃገሪቱ ተወዳጅ የሆነ ድንቅ ቢራ…” የሚሉ ሃረጎችን በመጠቀም ምርቶቻቸውን ሲያስተዋዉቁ ሰምተው ይሆናል፡፡ “በድፍን” ወይም “በመላ”  የሚሉትን የብዙሃን መገለጫ ቃላትን በመጠቀም አድማጩ ግለሰብ “እኔ ከብዙሃኑ ወደኋላ ቀርቻለሁ” የሚል ስሜት እንዲያጭርበትና ምርቱን ወይም አገልግሎቱን እንዲጠቀም የሚደረግበት ነው፡፡ ሁለተኛው አድማጩ ግለሰብ ራሱን ከሌሎች ጋር በማነጻጸር “እኔ እንደ ሌላው ተራ ተርታ ሰው አይደለሁም!” የሚል ስሜት እንዲፈጠርበትና ምርቱን ወይም አገልግሎቱን በመጠቀም ራሱን ከተራ ሰዎች እንደለየና ልዩ ክብር እንዳለው በማሰብ የሚኮፈስበት የአስተሳሰብ ህጸጽ (Appeal to Snobbery) በመባል የሚታወቀው ነው፡፡ ለምሳሌ ልዩ ልዩ የሙዚቃ ኮንሰርቶች በሚዘጋጁበት ጊዜ በአንደኛ ማዕረግና በተራ የመግቢያ ትኬት መሃል ያለውን እጅግ በጣም የገዘፈን የዋጋ ልዩነት በርካታ ሰዎች እንደ ተገቢ (reasonable) የዋጋ ልዩነት የሚቀበሉት በዚህ የአሰተሳሰብ ህጸጽ ተገፍተው ነው፡፡ ሶስተኛውና (Appeal to Vanity) በመባል የሚታወቀው የአስተሳሰብ ህጸጽ የሚፈጠረው ድርጅቶች ምርቶቻቸውን ታዋቂና በህዝብ ዘንድ ተወዳጅነት ካላቸው ስፖርተኞች፣ የፊልም ተዋናዮች፣የቁንጅና ንግስቶችና ሌሎች ዝነኛ ግለሰቦች ወይም ቡድኖች ጋር በማቆራኘት ህዝቡ ለግለሰቦቹ ወይም ለቡድኖቹ ያለውን አድናቆት ሳያስበው ወደሚተዋወቀው ምርትም እንዲያስተላልፍ በማድረግ ነው፡፡ እዚህ ላይ ልናስተውል የሚገባው በትክክለኛ የአስተሳሰብ መርህ መሰረት አንድን ምርት ወይም አገልግሎት ለመጠቀምም ሆነ ላለመጠቀም ከግምት ሊገባ የሚገባው የምርቱ ወይም የአገልግሎቱ የጥራት ደረጃና ለዚህም የሚቀርበው ዝርዝር ማሳመኛ እንጂ ራስን ከብዙሃኑ ህዝብ ጋር ማነጻጸር ወይም ምርትን ከዝነኛ ሰዎች ጋር በማቆራኘት የሚገኝ የስሜት እርካታ አለመሆኑን ነው፡፡   
በፓለቲካዊ የክርክር መድረኮች በተደጋጋሚ የሚደመጠው የአስተሳሰብ ህጸጽ ደግሞ የተከራካሪውን ግለሰብ ሀሳብ በመቃወም ፈንታ ራሱን ተከራካሪውን ግለሰብ በመንቀፍ ወይም  ስብዕናውን በልዩ ልዩ መንገድ በመንካት (against the person) የሚፈጸም ነው፡፡ ይህም በሦስት መንገድ ሊተገበር ይችላል፡፡ ለምሳሌ ባለፈው የአሜሪካ ፕሬዚደንታዊ ምርጫ ክርክር ወቅት ፕሬዚደንት ኦባማ ተቃራኒያቸው የአቶ ሩምኒን የምጣኔ ሃብት ፓሊሲ ሲያጣጥሉ ካቀረቧቸው በርካታ ተገቢ ማሳመኛዎች በተጨማሪ አቶ ሩምኒ “በፖሊሲያቸው ላይ ወጥ አቋም የሌላቸው ባለ ሁለት ምላስ ሰው ናቸው” በሚል ዘለፋ የተቀላቀለበት ንግግር ተቃራኒያቸውን ሲያሸማቅቁ ተመልክተናል፡፡ ምንም እንኳ ይህ አቀራረብ በብዙዎች ዘንድ ትክክል መስሎ ቢታይም  የተቃራኒን ሃሳብ እንጂ ተቃራኒውን ግለሰብ ራሱን በቀጥታ በመንቀፍ የሚቀርብ ማሳመኛ (Abusive) ለሚባለው መሰረታዊ የአስተሳሰብ ህጸጽ የተጋለጠ መሆኑን መረዳት ያስፈልጋል፡፡
በሌላ በኩል ሁለት ግለሰቦች በሃገራችን የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርት የማስተማሪያ ቀንቋ “በአፍ መፍቻ ወይስ በሁለተኛ” በሚል ክርክር በሚያደርጉበት አንድ መድረክ ላይ “የአፍ መፍቻን የትምህርት ቋንቋ ማድረግ አይገባም” የሚል አቋም ይዞ የሚሟገተው ግለሰብ በተቃራኒው ላይ  በማሳመኛነት ካነሳቸው ነጥቦች አንዱ “የአፍ መፍቻ ቋንቋን ደግፎ የቀረበው ተቃራኒው ግለሰብ እንዲህ ብሎ የሚከራከረው ‘ካድሬ’ ስለሆነ ነው እንጂ እውነታን ይዞ አይደለም!” የሚል ነበር፡፡ ከአመክንዮ ራቅ ብሎ ለሚያዳምጥ ሰው ጥሩ ማሳመኛ የቀረበ ቢመስለውም በትክክለኛ የአስተሳሰብ መርህ ሚዛን ግን (circumstantial) የሚባል ህጸጽ ተፈጽሟል እንላለን፤ ምክንያቱም የተገቢ አጸፋ ማሳመኛ (counter-argument) ዋና መገለጫ በቀጥታ ተቃራኒውን ግለሰብ ሃሳብ ውድቅ ማድረግ እንጂ ተቃራኒው ግለሰብ ስለሚገኝበት ሁኔታ በመተረክ አድማጭ ሃሳቡን እንዲያጣጥለው ማድረግ አይደለምና፡፡        
በተለይ ከፍተኛ ማህበራዊና ሙያዊ ኃላፊነት ላይ የሚገኙና ለሌሎች አርአያ መሆን የሚገባቸው ግለሰቦች የሚያስተምሩትና የሚተገብሩት ድርጊት ተቃራኒ የሆነበትን አጋጣሚ ፈልፍሎ በማውጣት ይህንን ድክመታቸውን እንደ ምክንያት ለራሳቸው መልሰው በማቅረብ መልስ አልባ አድርጎ ለማሳመን የሚሞከርበት የተሳሳተ የአስተሳሰብ መንገድ (you too) ይባላል፡፡ ለምሳሌ አንድ የድርጅት መሪ ሙስና ወንጀል ነው ብሎ እያስተማረ በሆነ አጋጣሚ እርሱ ራሱ በሙስና ተዘፍቆ ቢገኝ ከግለሰቡ ድርጊት ተነስተው ከተከታዮቹ አንዳንዶቹ ሙስና ወንጀል አይደለም የሚል መደምደሚያ ላይ ቢደርሱ ግንዛቤያቸው (you too) በተባለው የአስተሳሰብ ህጸጽ የተቃኘ ስለሆነ የተሳሳተ ነው ማለት ነው፡፡
በተለምዶ ማስቀየስ (Red Herring) በመባል የሚታወቀው የአስተሳሰብ ስህተት በርካታ ሰዎች በየዕለቱ ሲጠቀሙበት የሚስተዋል ሲሆን ይህም ግለሰቡ በተነሳው ርዕሰ ጉዳይ ዙሪያ ተገቢ ማስረጃ አቅርቦ በማሳመን ፈንታ ሃሳብን በእጅጉ የሚሰርቅ አጓጊ ርዕስ በመፍጠር የአድማጭን ሃሳብ በመበታተን የሚፈጸም ነው፡፡
በማስረጃዎቹና በድምዳሜው መሃል የተፈጠረው ግነኑኝነት ምናባዊ በሆኑ የምክንያትና ውጤት ትስስር ላይ ተመስርቶ ከሆነ ወይም ለአንድ ድምዳሜ ምክንያት የሆነውን ነገር እንደ ውጤት፤ ውጤቱን ደግሞ እንደ ምክንያት አዟዙሮ በማሰብ፤ ወይም ለአንድ ውጤት በርካታ ምክንያቶች ሊኖሩት እንደሚችል እየታወቀ አንድን ምክንያት ብቻ መርጦ በማቅረብ እንደ ዋናና ብቸኛ ምክንያት በማቅረብ ወይም አንድ ቀላል ኩነት (event) ሊያደርስ የሚችለውን ምናባዊ አደጋ ካለምንም ማስረጃ እጅግ በጣም አግዝፎ (አካብዶ) በማቅረብ አድማጭን አምታትቶ በምናባዊ ፍርሃት አሳቅቆ ለማሳመን በሚደረግ ሙከራ የሚፈጸም የአስተሳሰብ ስህተት የሀሰት ሰበብ (False cause) በመባል ይታወቃል፡፡
በሌላ በኩል በትክክለኛ ማሳመኛ ውስጥ የሚገኝ መደምደሚያ ከቀረቡት ማስረጃዎች መመንጨት እንዳለበት ይታወቃል፡፡ ይሁንና አንዳንድ ጀማሪ የጥናትና ምርምር ባለሙያዎች በጥናታቸው መደምደሚያ ላይ የሚያመጡትን ውጤት ጥናቱን ከመጀመራቸው በፊት በመገመት መላምታቸውን (hypothesis) በሚሰበስቡት መረጃዎች ላይ ተመስርተው በመፈተሽ ፈንታ ግምታቸውን በድምዳሜ ላይ በማስቀመጥ መረጃዎቻቸውን ጠምዝዘው የእነርሱን ሃሳብ በግድ እንዲደግፍ ለማድረግ በመሞከር የሚፈጠር ስህተት ፕሪዘምሽን ህጸጽ (Fallacy of Presumption) ይባላል፡፡ ይህ ህጸጽ በማሳመኛ ውስጥ የሚገኝንና መደምደሚያውን ሃሰት የማድረግ አቅም ያለውን አንድ ቁልፍ ማስረጃ በመሰወር ወይም በመደምደሚያው ላይ የተቀመጠውን ሃሳብ በማስረጃነት ደግሞ በማቅረብ ሊፈጸም ይችላል፡፡
በፍርድ ቤት ችሎት የምስክሮች አሰማም ሂደት ላይ በተደጋጋሚ የሚከሰቱ የአስተሳሰብ ስህተቶች በመስቀለኛ ጥያቄ አቀራረብ ላይ የተመሰረቱ ናቸው፡፡ ይህም መስቀለኛ ጥያቄ የሚያቀርበው አካል ለመስካሪው አንድ ውስብስብ ጥያቄ (complex question) ያቀርብና ምስክሩ ለዚህ ጥያቄ አንድ “አዎ” ወይም “አይደለም” የሚል መልስ እንዲሰጥ ይጠየቃል፤ ይሁንና ግለሰቡ የሚሰጠው ማንኛውም መልስ በሁለት መንገድ ሊተነተን የሚችል በመሆኑ ምስክሩ ባላሰበበት መንገድ ድምዳሜ በመስጠት ከምስክሩ አፍ ማረጋገጫ እንደተገኘ አድርጎ በማቅረብ የሚፈጠር ህጸጽ ወይም ማደናገሪያ ነው፡፡ ለምሳሌ ከዚህ በፊት ከማንም ጋር ግኑኝነት ላልነበረው ሰው “ከወንጀለኞቹ ጋር ማታ ማታ መገናኝት ትተሃል?” የሚል ጥያቄ ቢቀርብለትና ግለሰቡም “አዎ” የሚል መልስ ቢሰጥ አሁን ትቷል ነገር ግን ከዚህ በፊት ማታ ማታ ይገናኝ ነበር የሚል መደምደሚያ ይሰጥበታል፤ “አልተውኩም” ቢልም እንዲሁ ግኑኝነት አለኝ የሚል እምነት ቃል እንደሰጠ ይቆጠራል፡፡ ስለሆነም ትክክለኛ አስተሳሰብ ያለው ሰው “አዎ” ወይም “አልተውኩም” ከሚል መልስ ተቆጥቦ ጥርት ባለ ቋንቋ “እስከ ዛሬ ከማንም ጋር ግኑኝነት አልነበረኝም::” የሚል መልስ በመስጠት ራሱን መከላከል ይጠበቅበታል፡፡
በመጨረሻም በሰዋስው ምስስሎሽ (gramatical analogy) ባለቸው ቅርበት ሳቢያ የቡድንን መገለጫ ለነጠላ እንዲሁም ነገሮች በነጠላ ያላቸውን ባህርይ ለቡድን በማይገባ ሁኔታ በማስተላለፍ የሚፈጠር ህጸጽ እንገኛለን፡፡ ለምሳሌ “ኢትዮጵያውያን በጨዋነትና በእንግዳ ተቀባይነት የታወቁ ናቸው” ከሚለው የቡድን መገለጫ ተነስተን “ስለሆነም እያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ ጨዋና እንግዳ ተቀባይ ነው፡፡” የሚል መደምደሚያ ላይ ብንደርስ ወይም “በዋልዎቹ የእግር ኳስ ቡድን ውስጥ የሚገኝ እንዳንዱ ተጨዋች ምርጥ ነው፡፡” ከሚል የነጠላ ብቃት ተነስተን “ስለዚህ የዋልያዎቹ ቡድን ምርጥ የእግር ኳስ ቡድን ነው፡፡” የሚል ድምዳሜ ላይ መድረስ ስህተት ይሆናል፤ ምክንያቱም እንደ ቡድን ምርጥ ለመሆን ምርጥ ተጨዋቾችን ብቻ መያዝ በቂ ምክንያት አይደለምና፡፡
ከዚህም በተጨማሪ ጥንታዊ መጻህፍትን አንብቦ በትክክል የመተንተንና የመረዳት ሂደት (hermeunitics) ላይ የሚፈጠሩ በርካታ ህጸጾች (exegetical fallacies) የሚገኙ ሲሆን የጥንታዊ መጻህፍት ተመራማሪዎች (philologists) በተለይ የቅዱሳት መጻህፍት መምህራን፣ ሰባክያን ወይም የሥነ-መለኮት ምሁራን (theologians) በጥልቀት ሊያጠኗቸውና ራሳቸውን የተሳሳተ ትንታኔ ላይ ከመጣል ይጠብቁባቸው ዘንድ የትክክለኛ አስተሳበስ ጠበብት ይመክራሉ፡፡ 
                                ›››››…..‹‹‹‹‹

Monday, March 4, 2013

የአምላክን መኖር በፍልስፍና ማረጋገጥ ይቻላልን?



የሚታየውንና የማይታየውን ዓለም (universe) ካለመኖር ወደ መኖር ያመጣ፣ የሚቆጣጠር፣ ከሰው ልጆች እውቀትና ኃይል በላይ የሆነ አምላክ (God) የሚባል ላዕላይ ነገር (Being) የመኖሩ ወይም ያለመኖሩ ጥያቄ የዓለም ጠቢባንን ለበርካታ ዘመናት ሲያስጨንቅ የሰነበተና ዛሬም ድረስ ብዙዎችን በማወዛገብ ላይ የሚገኝ ዓቢይ ጥያቄ ነው፡፡
ለመሆኑ አምላክ አለ? መኖሩን ወይም አለመኖሩን ማረጋገጥ ይቻላል? እንዴት? በእምነት ብቻ? በፍልስፍና ? በሳይንስ? በእምነትና በፍልስፍና?
መልሱ እንደየዘመናቱና እንደየመላሾቹ ግለሰቦች ማንነት ሃማኖታዊ፣ ሳይንሳዊ ወይም ፍልስፍናዊ መልክ ሊኖረው ይችላል፡፡ ሃይማኖታዊው ምላሽ የአምላክን ህልውና በቅዱሳት መጻህፍት ምስክርነት (Scriptural truth) ወይም በምስጢራዊ መገለጽ (revelation) ማረጋገጥ ስለመቻሉ ሲያስረግጥ፤ ሳይንሳዊው ምልከታ ደግሞ የአምላክ ህልውና ጥያቄ በሳይንሳዊ መንገድ ሊረጋገጥ የሚችል (verifiable) አይደለም ይላል፡፡
የፍልስፍናን አተያይ ስንመለከት በአንድ በኩል በርካታ ፈላስፎች (theists) የአምላክን ህልውና በፍልስፍና ማረጋገጥ ይቻላል የሚል እምነት ሲያራምዱ ሌሎች ደግሞ (Atheists) በተቃራኒው ስለአምላክ አለመኖር በፍልስፍና ማረጋገጫ መስጠት ይቻላል በሚል በሁለት ጎራ ተከፍለው ለዘመናት ተካራክረዋል፤ አስተምረዋል፤ ጽፈዋልም፡፡ ከዚህም ባሻገር የአምላክን ሆነ የሌሎች መንፈሳዊ አካላትን ህልውና ማረጋገጥ ወይም ስለመኖራቸውም ሆነ ስላለመኖራቸው እርግጠኛ መሆን በጭራሽ አይቻልም የሚል አስተሳሰብ የሚያራምዱ ጎኖስቲካዊ አመለካከት ያላቸው ፈላስፎች  (agnostics) ማዕከላዊ የሆነ አቋም ይዘው ሁለቱ ጽንፎች ሲያቀራርቡ ኖረዋል፡፡  
በዚህ ክፍል ላይ “የአምላክን ህልውና በፍልስፍና ማረጋገጥ ይቻላል!” የሚለውን የፍልስፍና መስመር ተከትለው የቅዱሳት መጻህፍትን ምስክርነት ሳይሹ በአመክንዮ (reasoned argument) ላይ ብቻ ተመስርተው ለአምላክ ህልውና ፍልስፍናዊ ማረጋገጫ የሰጡ ፈላስፎችን ስራ ለማየት እንሞክራለን፡፡
የፈጣሪን ህልውና ከሚቀበሉና የአምላክን ህልውና በአመክንዮ ማረጋገጥ ይቻላል ብረው ከተከራከሩ ፈላስፎች መሃል አንሰልም፣ አኳይናስ፣ ኦውግስቲን ከክርስትናው፤ እንዲሁም አቬሲናና አቬሮስ ደግሞ ከእስልምናው ዓለም በአብነት የሚጠቀሱ ናቸው፡፡
አምላክ (God) የሚለው ቃል በበርካታ ፈላስፎች ስራዎች ውስጥ የምናገኘው ቃል ቢሆንም ቃሉን የተለያየ ሃሳብን ለመግለጽ ተጠቅመውበታል፡፡ ለምሳሌ ቴሊስ ውሃን፣ ሬኔ ዴካርት አምላክን፣ እንዲሁም አንሰልም፣ አኳይናስና ኦውግስቲን ደግሞ እግዚአብሔር የሚለውን ቃል ለማመልከት ተጠቅመውበታል፡፡
አንሰልም ከ1033-1109 ዓ.ም የነበረ ጣልያናዊ የስነመለኮት ምሁርና ፈላስፋ ሲሆን Monologion እና Proslogion በተባሉ ስራዎቹ የእግዚአብሄርን ህልውና ማረጋገጫ ፍልስፍና (ontological argument) ያቀረበ ነው፡፡
የአንሰልም የማረጋገጫ ፍልስፍና መዋቅር (framework) በአመክንዮ ላይ የተመሰረተ እምነት (reasoned faith) አንዲኖር የሚያስረግጥ ሲሆን ይህም እምነትን (faith) ከአመክንዮ (reason) የሚያስቀድመውን ነባር አስተሳሰብ የሚቃረን ነው፡፡
እንደ አንሰልም እምነት የክርስትና እምነት ዶግማ በአመክንዮ ላይ የተመሰረተ ነው፡፡ ምክንያቱም አምላክ ራሱ በላዕላይ አመክንዮ (supreme reason) የሚመራና በፈጠራቸው ፍጥረታት ላይ ይኸው ጥበቡ የሚገለጽ በመሆኑ ነው፡፡
በሌላ አነጋገር የሰው ልጆች ሁሉ አመክንዮ ከአምላክ የተሰጣቸው ስለሆኑና የእምነት መነሻ ምክንያትን መገንዘብ ስለሚችሉ አስቀድመው ህልውናውን የሚያምኑ ክርስቲኖችም ሆነ በቅዱሳት መጻህፍት የማያምኑ ግለሰቦች ሁሉ የእግዚአብሔርን ህልውና በአመክንዮ ላይ ብቻ ተመስርተው ማረጋገጥ ይችላሉ፡፡
አንሰልም ካቀረባቸው እርስ በርሳቸው የተያያዙ ሶስት ማረጋገጫዎች መካከል የመጀመሪያው ደረገው በዓለም ካሉ ጥሩ ነገሮች ሁሉ የበለጠ አንድ ጥሩ ነገር    (Supreme Good) መኖሩን ማረጋገጥ ነው፡፡ በመቀጠልም ይህንንም ማረጋገጫ ተንተርሶ ከሁሉም በላይ የሆነ ባህርይ ያለው (Supreme Nature) አካል መኖሩን ማረጋገጥ፤ በመጨረሻም በሁለተኛው ማረጋገጫ ላይ ተመርኩዞ በሁሉም ነገር ከሁሉም የበለጠ አካል (Most Excellent Being) ወይም አምላክ መኖሩን በማረጋገጥ ይደመድማል፡፡
የአንሰልም የመጀመሪው ማረጋገጫ የመልካሞች ሁሉ መልካም የሆነ ነገር  (Supreme Good) ስለመኖሩ ነው፡፡
በዓለማችን ላይ በርካታ ጥሩ ነገሮች አሉ፡፡ የጥሩነታቸውን መጠን ስናወዳድር ግን ጣት ከጣት ይበልጣል እንደሚባለው አንዱ ጥሩ ነገር ከሌላው መብለጡ የግድ ነው፡፡ ለምሳሌ አንድ ፈረስ ከሌላው፤ መልካም ፈረስ የሚባለው ከጥንካሬውና ከፍጥነቱ አንጻር ነው፡፡ ይሁንና ጠንካራና ፈጣን የሆነ ዘራፊ ግን መልካም ሰው ሊባል አይችልም፤ መጥፎ እንጂ፡፡ በመሆኑም አንጻራዊ የሆነ መልካምነት (Good) ያላቸው ነገሮች በራሱ (Intrisitically) መልካም ከሆነ ነገር አንጻር ያነሰ መልካምነት ያላቸው ነገሮች ናቸው፡፡ በሌላ አነጋገር መልካም እንጨት፣ መልካም ፈረስ፣ መልካም ሰው ሁሉም በመጠኑ መልካም የሆኑ ነገሮች ናቸው፡፡ መልካም ናቸው ብለን በደመደምንበት መስፈርት አሰሳ ብናካሂድ ለእነርሱ አቻ የሆኑ ሌሎች መልካም ሰዎች፣ ፈረሶችና ሰዎችን መዘርዘር እንችላለን፡፡ ነገር ግን መልካም እንጨት ከመልካም ፈረስ ወይም ከመልካም ሰው ጋር አንድ ዓይነት የመልካምነት ባህርይ ስለሌላቸው የአንዱን መልካምነት ከሌላው ጋር ማወዳደር ትክክል አይሆንም፤ ሁሉም ከአቻዎቻቸው ጋር ይነጻጸራሉ እንጂ፡፡
በመሆኑም አንዱ መልካም ነገር ከሌላው መብለጡ ግድ ከሆነና ከላይ የተመለከትናቸው ነገሮች መልካምነት አንጻራዊ ነው ከተባለ ከመልካም ነገሮች ሁሉ የላቀ መልካም የሆነ፣ ለመልካምነቱ አቻ የሌለው መልካምነቱም ከራሱ የመነጨ (Intrisitic) አንድ አካል አለ ብሎ መደምደም አመክኗዊ ይሆናል፡፡ መልካም ነገሮች ሁሉ እንደሚወደዱ ሁሉ ይህ የመልካሞች ሁሉ መልካም (Supreme Good) የሆነ ታላቅ አካል ከመልካሞች ሁሉ የበለጠ ሊወደድ ይገባል ማለት ነው፡፡      
የአንሰልም ሁለተኛው ማረጋገጫ ከሁሉም በላይ የሆነ (ልዑል) ባህርይ ያለው አካል (Supreme Nature) ስለመኖሩ የሚያትት ነው፡፡   
በዓለማችን ላይ የሚገኙ የሚታዩና የማይታዩ ነገሮች ካለመኖር ወደመኖር ሲመጡ ወይ ከሆነ ነገር (out of something) ተገኝተዋል አልያም ከምንም (out of nothing) የተገኙ ናቸው፡፡
በሳይንሳዊው ሮጀርስ መርህ ደግሞ “Nothing comes from nothing” ከምንም የተገኘ ምንም ነገር የለም፡፡ ስለሆነም በዓለማችን ላይ የሚገኙ ነገሮች ሁሉ የተገኙት ከሆነ ነገር (something) ነው ማለት ነው፡፡
ዓለማችን ከሆነ ነገር ተገኝታለች ብለን ካመንን የሚታዩና የማይታዩ ነገሮች ሁሉ የተገኙት ወይ ከአንድ ነገር ነው አልያም ከብዙ ነገሮች ነው ማለት ነው፡፡
ዓለማችን የተገኘችበት ብዛት ያላቸው ነገሮች ካሉ ለእነዚህ ነገሮች ሁሉ አንድ ብቸኛ አስገኚ አላቸው፤ አልያም እንዳንዱ ነገር በራሱ የተገኘ ነው፤ወይም ደግሞ አንዱ ከሌላው የተገኘ ነው፡፡
እያንዳንዱ ነገር በራሱ የተገኘ ነው እንዳንል ምንም ነገር ከምንም ሊገኝ አይችልም፡፡ አንዱ ከሌላው የተገኘ ነው ብንልም አስገኚውን ነገር ያስገነውን ሌላ አስገኚ ማግኘት ግድ ይለናል፡፡ ይህም ብዛት ያላቸውን ነገሮች ያስገኘ፤ በራሱ የተገኘ አንድ ኃይል አለ ወደሚለው ድምዳሜ ያስገባናል፡፡
ብዛት ያላቸው ነገሮች የተገኙበት አንድ አካል አለ ማለት የሚታዩና የማታዩና የማይታዩ ነገሮች በሙሉ የተገኙት በራሳቸው ሳይሆን ከእነርሱ ውጪ በሆነ አካል ነው ማለት ነው፡፡ ከራሱ ውጪ በሆነ አካል የተገኘ ነገር በሙሉ በራሱ ከተገኘ ነገር አንጻር ዝቅተኛ ደረጃ ላይ የሚገኝ ወይም ያነሰ ነው፡፡ ስለዚህ በራሱ ከተገኘው አካል ውጪ ያሉ ነገሮች በሙሉ በባህርቸው በራሱ ከተገኘው አካል ያነሱ  ናቸው፡፡ ከዚህም በመነሳት በራሱ የተገኘው አካል ታላቅና (Great) ከሁሉም በላይ የሆነ (ልዑል) ባህርይ (Supreme Nature)  አለው ማለት ነው፡፡ ይህም   አንሰልም  ከሁሉም በላይ እጅግ በጣም መልካም የሆነ አካል (Excellent Being) ስለመኖሩ የሚያትተውን ሶስተኛ ማረጋገጫ ያስከትላል፡፡ 
እንደ ሰር ጀምስ ፍሬዘር ብያኔ አምላክ ማለት የመጀመሪያው ኃያል አስገኚ፣ ዓለምን የሚቆጣጠር፣ ከሰዎች እውቀትና ከተፈጥሮ ህግ በላይ የሆነ አካል ነው፡፡ እንደ አንሰልም እምነት አምላክ ማለት ከእርሱ በላይ ማንም ምንም ኃያልና መልካም ቀዳሚ የሌለ አካል ማለት ነው፡፡  የዚህ ዓይነት አካል (Being) ስለመኖሩ በእእምሮአችን ውስጥ ሊታሰብ ይችላል፤ በሁለተኛው ማረጋገጫ የተመለከተውን ከሁሉም በላይ የሆነ (ልዑል) ባህርይ ያለው አካል (Supreme Nature) በመኖሩ የተስማማ ሰው በትክክለኛ የአስተሳሰብ ቀመር (Logic) ስሌት መሰረት ይህ አምላክ አለ ብሎ መደምደሙ ተገቢ ይሆናል፡፡
ስለአምላክ ህልውና በሁለተኛ ደረጃ የሚገኘው የፈላስፎች ማረጋገጫ ከስነፍጥረት አንጻር የቀረበ ማሳመኛ (cosmological argument) ነው፡፡ በመካከለኛው ዘመን የነበረው የቶማስ አኲናስና በ18ኛው ክፍለ ዘመን የተነሳው ሳሙኤል ክላርክም ስራዎች ለዚህ ፍልስና ማሳያዎች ናቸው፡፡
አኲናስም ሆነ አብዛኞቹ የዚህ ፍልስፍና አራማጆች የሚያቀርቡት ማሳመኛዎች የሚከተለውን የአመክንዮ መዋቅር የተከተለ ነው፡፡
ማንም ሰው ስነ-ፍጥረትን ወይም በጊዜና በቦታ ተወስኖ የሚታየውና የማይታየውን ዓለም ህልውና ይገነዘባል፡፡ ይህ ዓለም ደግሞ ራሱን በራሱ አስገኘ ማለት አይችልም፡፡ ይህ እጅግ በጣም ውስብስብ የሆነ ዓለም ከምንም ተገኘ ማለት ደግሞ አይቻልም፡፡ ከሌላ ከሆነ ግዑዝ ነገር ተገኘ ካልን የመጨረሻውን አስገኚው ለማግኘት መጨረሻ ወደሌለው የአስገኚና የተገኚ ክትትሎሽ ውስጥ እንገባና ያለመልስ እንቀራለን፡፡ ስለዚህ ይህ ዓለም ከጊዜና ከቦታ ውጪ በሆነ ያልተገኘ ግን የሚያስገኝ አንድ የመጨረሻ አካል የተገኘ ነው፡፡
በዚህ ፍልስፍና በቀዳሚነት የሚታወቀው ጣልያናዊው ፈላስፋና የሥነ-መለኮት ምሁር ቅዱስ ቶማስ አኲናስ (1225-1274) “Summa Theologiae” በተባለ መጽሐፉ የፈጣሪን ህልውና በአምስት መንገድ ሊረጋገጥ እንደሚችል አስረድቷል፡፡
በመጀመሪያ ደረጃ ማንም ሰው ለማየትና ለማረጋገጥ እንደሚችለው በዓለም ላይ የሚገኙ የተወሰኑ ነገሮች ሁልጊዜ በእንቅስቃሴ ላይ ናቸው፡፡ ማንኛውም ተንቀሳቃሽ ነገር የሚንቀሳቀሰው በሌላ አንቀሳቃሽ ነው፤ ምክንያቱም እንቅስቃሴ የሚፈጠረው አንድን የመንቀሳቀስ አቅም (potentiality) ያለውን ነገር ወደ ተግባራዊ እንቅስቃሴ (actuality) መለወጥ የሚችል ኃይል ሲኖር ብቻ ነው፡፡ አንድና ተመሳሳይ ነገር ደግሞ በራሱ አንቀሳቃሽም ተንቀሳቃሽም መሆን አይችልም፡፡ ለምሳሌ እንጨት የሚፋጅ ሞቃት የመሆን አቅም አለው ነገር ግን ወደሞቃትነት የሚለወጠው እሳትን ሲያገኝ ብቻ ነው፡፡ስለሆነም ማንኛውም የሚንቀሳቀስ ነገር የግድ በሌላ ሊንቀሳቀስ ይገባል ማለት ነው፡፡ አሁን የምናያቸው የሚንቀሳቀሱ ነገሮች በቅርብ የምናውቀው አንቀሳቃሽ ቢኖራቸውም ለዚያ አንቀሳቃሽ ሌላ አንቀሳቃሽ አለው፡፡ ይህም በመጨረሻው ወደ መጀመሪያው አንቀሳቃሽ እርሱ ግን በሌላ በማንም ወደማይንቀሳቀሰው አንቀሳቃሻ ያደርሰናል፤ እርሱን ሁሉም አምላክ ብለው ይረዱታል፡፡
ሁለተኛ በዚህ በሚታየው ዓለም የምክንያትና (cause) የውጤት (effect) ትስስር ስርዓት እናያለን፤ አንዱ ነገር ቀጥተኛ ምክንያት (efficient cause) ሆኖ ሌላኛውን ሲያንቀሳቅሰው ማለት ነው፡፡ ለአንድ ውጤት አንድ ወይም ከአንድ በላይ ምክንያቶችን በመሃል ላይ ልናገኝ እንችላለን፡፡ እነዚህን ማዕከላዊ ምክንያቶች ሊኖሩ ይችላሉ፡፡ አሁንም አንዱ ምክንያት ሌላውን አስገኘ እያልን ብንቀጥል የትየለሌ (infinity) ውስጥ እንገባለን፤ ይህም መልስ አይሆንም፡፡ ስለዚህም አንድ የመጀመሪያ ቀጥተኛ ምክንያት (first efficient cause) መኖሩን መቀበል ግድ ይለናል፤ ይህም አምላክ የሚል መጠሪያ የተሰጠው ነው፡፡
በሌላ በኩል በዓለም ላይ ያሉ ነገሮችን ስንመለከት እንዴት ሊሆን ቻለ (How possible) ብለን እንጠይቃለን፤ ነገሮቹ ሊኖሩ ወይም ላይኖሩ ይችሉ ነበርና፡፡ ነገሮችን ካለመኖር ወደ መኖር በማምጣት ረገድ ምንም እንኳ በርካታ መካከለኛ ምክንያቶችን ብንመለከትም በመጀመሪያ የግድ አንድ በራሱ የተገኘ ኃይል (necessity) ሊኖር እንደሚገባ የታመነ ነው፡፡
ከዚህም ሌላ የተፈጥሮን ሥርዓት ደረጃ (gradation) ስንመለከት አንዱ ነገር ከሌላው የበለጠ ወይም ያነሰ ሆኖ እናገኘዋለን፡፡ በአንድ ዋና ምድብ (genus) ውስጥ የምናገኘው የመጨረሻው ነገር የምድቡ አስገኚ ነው፡፡ እሳት የሞቃት ነገሮች ምድብ የመጨረሻው ደረጃ እንደመሆኑ መጠን የሞቃት ነገሮች ሁሉ አስገኚ ነው፡፡ ስለዚህም ከጎዶሎነት ወደ ፍጹምነት ካለማወቅ ወደ ጠቢብነት ከፍ እያልን ስንመጣ የምናገኛቸው የመጨረሻ የፍጹማን ፍጹም የመልካሞች ሁሉ መልካም የጠቢባን ሁሉ ጠቢብ የምክንያቶች ሁሉ ምክንያት አምላክ ብለን የምንጠራው ነው፡፡
በመጨረሻም ከዓለም አስተዳደር (governance of the world) የቀረበውን ማሳመኛ ስንመለከት በሚሰራው ስራ ዙሪያ እውቀት ያነሰው ማንኛውም አካል የተሻለ እውቀትና ጥበብ ባለው ሌላ አካል ካልታገዘ ወይም ካልተመራ በቀር ውጥኑን ከግብ ለማድረስ እንደማይችል ሁሉ ይህቺን ዓለምና በውስጧ ያሉ ነገሮች የተፈጠሩበትን ዓላማ ግብ መምታት እንዲችሉ ዓለምን በዓላማና በጥበብ የሚመራ አንድ እጅግ አዋቂና ጠቢብ አካል (intelligent being) አለ ብሎ ማመን ተገቢ ይሆናል፡፡             
ስለአምላክ ህልውና በሶስተኛ ደረጃ የቀረበው (Teleological Argument) በመባል የሚታወቀው ሲሆን ይህም አኲናስ በመጨረሻ ደረጃ ካስቀመጠው ማረጋገጫ ጋር የሚቀራረብ ነው፡፡ የዚህ ማሳመኛ ዋና የፍልስፍና መዋቅር ይህቺ ዓለም ያለ አንድ ዓላማ (purpose)፣ ግብና (goal) አስገኚ (designer) በዘፈቀደ የተገኘች አለመሆኗን ማረጋገጥ ነው፡፡
የዊሊያም ፓሊ (William Paley) 1743-1805 የእጅ ሰዓት ምሳሌ (watch analogy) ማሳመኛ በዚህ ረገድ ቀዳሚውን ስፍራ የያዘ ነው፡፡ ለምሳሌ አንድ የእጅ ሰዓት መሬት ላይ ወድቆ ቢገኝ መሬት ላይ ወድቆ እንደተገኘ ድንጋይ እንዲሁ ያለዓላማና ያለአስገኚ ተገኘ ብለን ማሰብ አይገባንም፤ ምክንያቱም የተገኘው ሰዓት አንድ በሰዓት ህንድስና ጥበብ በተካነ መንዲስ (designer) በጥንቃቄ በውስጡ ያሉት ልዩ ልዩ ጥርሶችና ተገጣጣሚ አካላት እርስ በርስ ተቀናጅተው በቀን አስራ ሁለት ሰዓት፣ በሰዓትና በደቂቃ ደግሞ ስልሳ ጊዜ እየተሽከረከረ ሳይዛነፍ በትክክል ጊዜን ለመለካት ዓላማ የተሰራ ነው፡፡
በተመሳሳይ ሁኔታ በዓለም ውስጥ የሚገኙ እጅግ ውስብስብና አስደናቂ በሆነ መንገድ እርስ በርሳቸው የተሳሰሩ ነገሮች ለምሳሌ ረቂቅና ግዙፍ፣ እንስሳትና ዕጽዋት፣ ፀሐይና ጨረቃ፣ አንጎልና ልብ፣ አጥንትና ጅማት፣ፕላኔቶችና ምህዋሮቻቸው የመሳሰሉት ነገሮችም እንዲሁ ያለዓላማና ያለአስገኚ  በዘፈቀደ ተገኙና የሚሰሩ ናቸው ብሎ ማሰብ ስህተት ይሆናል፡፡ ሰዓቱን የሰራውን መሃንዲስ ማንነት በትክክል አለማወቃችን ለሰዓቱ አስገኚ የለውም ለማለት እንደማያበቃን ሁሉ የአምላክን ማንነት በትክክል አለመረዳታችንም ለዝች ዓለም አስገኚና መጋቢ አምላክ የላትም፤ እንዲሁ የተገኘች ናት ለማለት በቂ ምክንያት አይሆንም ማለት ነው፡፡
እስከ አሁን ከተመለከትናቸው የፈጣሪ ህልውና ማሳመኛዎች በተለየ መልኩ የምናገኘውና የአንዳንድ ግኖስቲክ ፈላስፎች አቋም ከሆነው ፍልስፍና አንዱ የፓስካል ዌይጀር (Pascal’s Wager) ማሳመኛ በመባል ይታወቃል፡፡ እንደ አስራ ስድስተኛው ክፍለ ዘመን ፈረንሳዊው ፈላስፋና ሳይንቲስት ብሌይዝ ፓስካል እምነት አምላክ አለ ወይም የለም ብሎ በርግጠኝነት መናገር አይቻልም፡፡ ፍልስፍናም ሆነ ሳይንስ ለርግጠኝነታችን ድጋፍ ማቅረብ አይችሉም፡፡ በአምላክ ህልውና ጥያቄ ውስጥ እንደ ውርርድ ቁማር (Wager) የተሻለ ያዋጣል ብለን የምናስበውን አቋም ደግፈን በተስፋ ከመጠባበቅ የተሻለ ምርጫ አይኖረንም፡፡ እርግጠኛ ባልሆንበት ሁኔታ አምላክ የለም የሚለውን አቋም ብንይዝና ግምታችን የተሳሳተ ቢሆን ከፍተኛ ዋጋ እንከፍላለን (infinite suffering) ግምታችን ትክክል ሆኖ ቢገኝ ግን የምናገኘው ዋጋ ግን በዘመን የተወሰነ ምድራዊ ደስታ (finite earthly happiness) ነው፤ ነገር ግን እርግጠኛ ባንሆንም እንኳ አምላክ አለ የሚለውን አቋም ብንደግፍ ግምታችን ትክክለኛ ሆኖ ከተገኘ የምናገኘው ሽልማት  እጅግ ከፍ (infinite salvation) ሲሆን የምናጣው እጅግ በጣም አነስተኛ ነገር ነው፡፡ በውርርድ ቁማር ውስጥ ከተሸነፍክ ያስያዝከውን ነገር በሙሉ ታጣለህ፤ ካሸነፍክ ግን ምንም የምታጣው ነገር አይኖርም፡፡ “If you win you win everything, if you lose you lose nothing.” ስለሆነም በአመክንዮ ለሚመራ ሰው በአምላክ ህልውና ካለማመን ይልቅ ማመን የተሻለ ነው፡፡      
›››››…..‹‹‹‹‹

አፍሪካውያን ፍልስፍና አላቸውን?


I wrote for Addis Admas Newspaper (Yekatit 2,2005E.C) 
ብዙዎች አጠቃላይ የፍልስፍናን አጀማመር ከአውሮፓውን ጋር በተለይ ደግሞ ከክ.ል.በፊት በ580 ዓ.ዓ ገደማ ከተነሱ ቀደምት ግሪኮች ጋር በቀጥታ የተያያዘ ስለመሆኑ በአንድ ድምጽ ይስማማሉ፡፡
አንዳንዶች ከዚህም አልፈው ፍልስፍና በተወሰኑ የዓለም ክፍሎች ለሚኖሩ፣በቆዳ ቀለም ተለይተው ለሚታወቁ የሰው ዝርያዎች ብቻ የተሰጠ ጸጋ መሆኑን በድፍረት ይናገራሉ፡፡ ለምሳሌ ኢማኑኤል ካንት በጂኦግራፊካል ስነ-ሰብ (Geographical Anthropology) ጥናቱ የሰውን ዘር ከአካባቢ አንጻር በቆዳቸው ቀለም የአስተሳሰብ ችሎታን በደረጃ ከፋፍሎ ባስቀመጠበት አንቀጽ አፍሪካውያንንና አሜሪ-ኢንዲያንን የመጨረሻዎቹ ተርታ ላይ አሰልፏቸዋል፤ ጀርመናውያንን (አውሮፓውንን) የመጀመሪያ አድርጎ ማለት ነው፡፡
ሌቪ ብሩልና ሄግል የተባሉት አውሮፓውያን የስነ-ሰብ (Anthropology) ተመራማሪዎችም እንዲሁ በጹሁፎቻቸው አፍሪካውያንና አሜሪ-ኢንዲያን እንደ አውሮፓውያን በአመክንዮ ማሰብ ስለማይችሉ (savage, premature or primitive mentality) የራሳቸው ባህልና ታሪክ የላቸውም፤ ለፍልስፍናም ብቁ አይደሉም ሲሉ ተደምጠዋል፡፡ ለመሆኑ ፍልስፍና ለአውሮፓውያን ብቻ የተሰጠና በአውሮፓውያን፣ በጀርመኖች ወይም በግሪኮች የተጀመረ ጥበብ ነው ?
ይህን ጥያቄ ለመመለስ ጥያቄውን በጥሞና ማስተዋል ግድ ይላል፤ በተለይ በፍልስፍና መጀመርና በፍልስፍና ትምህርት መስፋፋት መካከል ያለውን ልዩነት በተመለከተ፡፡ የፍልስፍና አጀማመርን ለመረዳት የፍልስፍናን ምንነት ማወቅ ይኖርብናል፡፡
ፍልስፍና አንድ እውነት ወይም ድምዳሜ ላይ ለመድረስ አንድን መሰረታዊ ጥያቄ ማንሳት ወይም በአመክንዮ ላይ ተመስርቶ ለመመለስ የሚደረግ ጥልቅ የአስተሳሰብ ሂደት ነው፡፡ ይህ ጉዳይ ደግሞ በዘር፣ በጎሳ፣ በቆዳ ቀለም ወይም በአካባቢ ሳይለይ ለሰው ልጆች ሁሉ በተፈጥሮ የተሰጠ የሰብዓዊ ፍጡርነት መገለጫ ነው፡፡ እ.አ.አ በ335ዓ.ዓ የተነሳው የግሪኩ ፈላስፋ አሪስጣጣሊስ (Aristotle) ሰው በምክንያታዊነት ማሰብ የሚችል እንስሳ ነው “Man is a rational animal.” ማለቱ ፍልስፍና የሰውነት መገለጫ መሆኑን የሚያመላክት ነው፡፡
ፍልስፍና ከሰው ልጆች ወደዝች ዓለም መምጣት ጋር ተያይዞ የተጀመረ የሰውነት መለያና የሰዎች መደበኛ ተግባር እንጂ ከጊዜ በኋላ በአውሮፓ የተፈጠረ ታሪክ አይደለም፡፡
አንሰልም እንደተባለው የመካከለኛው ዘመን አውሮፓዊ ክርስቲያን ፈላስፋ ማሳመኛ (argument) አምላክ በባህርይው ምክንያታዊ ስለሆነና መጽሐፍ ቅዱስ ደግሞ ሰው በአምላክ አምሳል መፈጠሩን ስለሚናገር፤ በአምላክ አምሳል የተፈጠረው የሰው ዘር በሙሉ እንደ አምላኩ ምክንያታዊ ነው የሚለው ድምዳሜ ምክንያታዊ ነው፡፡ ከዚህም ባሻገር በኦሪት ዘፍጥረት እንደተጻፈው አምላክ ለመጀመሪያው ሰው አዳም ትዕዛዝ ከሰጠበት ጊዜ ጀምሮና አዳም “መልካምና ክፉውን ከምታስታውቀው ዛፍ በበበላህ ቀን  ሞትን ትሞታለህ” የተባለበትን እውነተኛ ምክንያት ምንነት የማወቅ  ውስጣዊ ጥያቄ ከተፈጠረበት ጊዜ ጀምሮ በሰው ልጆች ዘንድ የፍልስፍና ጥያቄ ተጀምሯል ማለት ይቻላል፡፡ ይህንንም የሰው ልጅ ለፍልስፍና ያለውን ብርቱ ፍላጎት አዳምና ሄዋን ከአምላካቸው ትዕዛዝ ይልቅ በእባብ በቀረበላቸው አመክኖአዊ ማብራሪያ በመማረካቸውና፤ የተሰጣቸውን ማስጠንቀቂያም ለመሻር በመብቃታቸው እንረዳለን፡፡
በአጠቃላይ የፍልስፍና አጀማመር ከሰው ልጅ ማሰብ መጀመር ጋር የሚያያዝ በመሆኑ፤ በዓለም ታሪክ ቀደምት ስልጣኔ የነበራቸው ህዝቦች በሙሉ በተለይ ሜሶፖታሚያ፣ ግብፅ፣ እንዲሁም ቻይናና ህንድን የመሳሰሉ የሩቅ ምስራቅ ህዝቦች ሁሉ የራሳቸው ፍልስፍና ስልጣኔ ታሪክ ያላቸው ስለሆኑ፤የፍልስፍና ጀማሪነትንም ሆነ ባለቤትነትን ለግሪኮች ብቻ መስጠት ስህተት ይሆናል፡፡ ይልቁንም ጥንታዊ ግሪኮች በምእራባውያን የፍልስፍና ታሪክ (History of Western Philosophy) ውስጥ ቀዳሚውን ስፍራ መያዛቸውን ማስረገጥ ይገባል፡፡
ፍልስፍና ወይም ምክንያታዊነት ለሰው ልጆች ሁሉ የተሰጠ ሃብት ነው ስንል ግን በዓለም ላይ ያሉ ህዝቦችና ግለሰቦች በሙሉ ተመሳሳይ የፍልስፍና ባህል አላቸው ማለታችን ግን አይደለም፡፡ በተፈጥሮ የተሰጠን የፍልስፍና ዝንባሌ በግለሰቦች ንቃተ-ህሊና፣ ልምምድና የፍልስፍና ትምህርት ወይም በማህበረሰቡ ባህልና የጋርዮሽ ፍልስፍና ተጽዕኖ ሊጎለብት ወይም ሊዳፈን ይችላል፡፡
ይህም ማለት አከራካሪው ነጥብ የፍልስፍና አጀማመርና ባለቤትነት ሳይሆን የፍልስፍና በማህበረሰቡ ውስጥ የሚሰጠው የክብር ቦታ ወይም ጥልቅ ምክንያታዊነት እንደ ባህል የመዳበሩና ያለመዳበሩ ጉዳይ ነው፡፡
አንዳንድ ህዝቦች ስለፍልስፍና ካላቸው የዕውቀት ማነስና የግንዜቤ መዛባት የተነሳ ለመስኩ ጭፍን ጥላቻን በማዳበር ፍልስፍናን ሲሸሹት፣ የፍልስፍና ዝንባሌ ያላቸውን ግለሰቦችን ሲያሳድዱ፣ የጻፏቸውንም መጻህፍት ሲቃጥሉ ኖረዋል፤ በዚህም ምክንያት በእንደነዚህ ዓይነት ማህበረሰብ ውስጥ ፍልስፍናና ስሁል መስተሐልይ (critical thinking) በበቂ ሁኔታ ሊዳብር አይችልም፡፡
በሌላ በኩል ደግሞ ጥቂት ግለሰቦች ለፍልስፍና ወይም ለእውነት ካላቸው ፍቅር የተነሳ በከፈሉት የህይወት መስዋዕትነት ፍልስፍና በማህበረሰቡ ዘንድ በስፋት ለታወቅና በግለሰቦች የህይወት ፍልስፍና  ውስት ትልቅ ስፍራ ለማግኘት ከመቻሉም ባሻገር እነዚሁ ጥቂት ግለሰቦች ፍልስፍናቸውን በቃል አስተምረው ህዝባቸውን ለማንቃትና በጻፏቸው መጻህፍት ደግሞ ለሌላው ህዝብ ለመትረፍ ችለዋል፡፡
ከዚህ አንጻር በጥቅሉ አውሮፓውያንን በነጠላ ደግሞ ጥንታውያን ግሪኮችን የሚበልጥ አይኖርም ለማለት እደፍራለሁ፡፡ እንግሊዛዊው ፈላስፋ በርትርን ረስል “The History of Western Philosophy” በሚለው መጽሃፉ ላይ በአውሮፓውያን የፍልስፍና ታሪክ የመጀመሪያው ፈላስፋ በመባል ከሚታወቀው ቴሊስ (Thales) ጀምሮ በየዘመናቱ በቃልና በጽሁፍ የተላለፈውን የፍልስፍና ዕድገት ይተርካል፡፡
በዓለም የሚገኙ ነገሮች የተገኙበትን ጥንተ ቁስ (Primordial matter) ምንነትና ካለመኖር ወደ መኖር መምጣትና ከመኖር ወደ አለመኖር የመመለስን የተፈጥሮ ምስጢር ላይ ለመድረስ ይነሳ የነበረውን የዲበአካላዊነት (metaphysical) ጥያቄ በምዕራብም ሆነ በምስራቅ ያሉ ህዝቦች በየዘመናቱ በየራሳቸው መንገድ ለመመለስ ሞክረዋል፡፡
ለምሳሌ ምዕራባዊው ፈላስፋ ቴሊስ በ546 ዓ.ዓ ገደማ ዓለም የተገኘችበት ንጥተ ቁስ ውሃ መሆኑን ተናግሯል፤ተከታዩ አናግዚሜንስ ጥንተ ቁሱ ንፋስ ነው ሲል ሄራክሊተስ ደግሞ እሳት ነው ብሎ ነበር፣ ፓይታጎረስም በተለየ ሁኔታ የዓለም መገኘት ምስጢር ቁጥሮች ናቸው ብሎ ያምን ነበር፡፡
አፍሪካውያን ፍልስፍና አላቸው? የሚለው ጥያቄ አፍሪካውን እንደ ሰው ያስባሉ? መሰረታዊ የፍልስፍና ጥያቄዎችን ያነሳሉ ? የተነሳባቸውን ጥያቄ ለመመለስ በራሳቸው መንገድ ይፍጨረጨራሉ? ከሚሉት ጥያቄዎች ተለይቶ አይታይም፡፡ መልሱም አወንታዊ ነው፡፡ ምንም እንኳ የፍልስፍና መሰረታዊ ጥያቄዎች በሰው ልጆች ሁሉ ዘንድ በጋራ የሚነሱ ቢሆኑም ጥያቄዎቹ የሚመለሱበት መንገድ ግን ከግለሰብ ግለሰብ፤ ከአህጉር አህጉር ሊለያይ ይችላል፡፡
እንደ ኬንያዊው ፈላስፋ ኦዴራ ኦሩካ እምነት አፍሪካውያን ከአውሮፓውን በተለየ ሁኔታ ፍልስፍናቸውን በአራት የተለያዩ መንገዶች ሊከናውኑ ይችላሉ፡፡
የመጀመሪያው ኢትኖፊሎሶፊ (ethno philosophy) በመባል የሚታወቅ ሲሆን ይህም የአፍሪካውያን ፍልስፍና እንደ ቋንቋና ሃይማኖት በመሳሰሉ የማህበረሰቡ  ቱባ ባህላዊ እሴቶች ውስጥ በገቢር የሚገለጽ ነው የሚል ነው፡፡ ለምሳሌ በልዩ ልዩ የኢትዮጵያ ብሄር ብሄረሰቦችና ህዝቦች ቋንቋ ውስጥ የሚገኙ ምሳሌያዊ አነጋገሮች የማህበረሰቡ ፍልስፍና አጭር መገለጫዎች ናቸው፡፡
በሌላ በኩል አክሲማሮስ የተባለው ጥንታዊ የኢትዮጵያ ብራና የሃይማኖት መጽሐፍ ዓለም ስለተገኘበት ጥንተ ቁስ ምንነት ሲያብራራ አምላክ በመጀመሪያው ቀን በዕለተ እሁድ አራቱን ባህርያተ ሥጋ በመባል የሚታወቁትን ጥንተ ቁሶች ማለትም ንፋስ፣ እሳት ውሃ እና መሬት (አፈርን) በአርምሞ መፍጠሩን ይተርካል፡፡ ይህም ምዕራባውያኑ ፈላስፎች እነ ቴሊስ፣ አናግዜሜንስና ሄራክሊተስ ሃሳብ ጋር እንዲሁም በኦሪት ዘፍጥረት “አምላክም ሰውን ከምድር አፈር አበጀው” ከሚለው ኃይለ ቃል ጋር ተቀራራቢ ሆኖ እናገኘዋለን፡፡
ፊሎሶፊክ ሳጋሲቲ (Philosophic Sagacity) ሁለተኛው የአፍሪካውያን ፍልስፍና መልክ ሲሆን ይህም በማህበረሰቡ ውስጥ ለየት ያለ የፍልስፍና ዝንባሌ ባላቸው የማህበረሰቡ ነባር አባላት የሚካሄድ የፍልስፍና ተግባር ነው፡፡ ይህ የሳጋሲቲ ፍልስፍና እነዚህ ግለሰቦች በማህበረሰባቸው ግለሰባዊና ማህበረሰባዊ አስተሳሰብ ዙሪያ የሚያሳዩት ምልከታ፣ ወይም በሚያቀርቡት የሰላ ትችትና አማራጭ አስተሳሰብ የሚገለጽ ነው፡፡ በኢትዮያ ውስጥ በስፋት የሚታወቁት የአውራ አምባ ማህበረሰብ መሪ ዙምራ አስተሳሰብን ለዚህ ዓይነቱ ፍልስፍና ዓቢይ ምሳሌ ይሆናል፡፡
የፓለቲካ ርዕዮተ ዓለም ፍልስፍና         (Politico- ideological Philosophy) ሶስተኛው የአፍሪካውያን ፍልስፍና መገለጫ ሲሆን በተለይ በቅኝ ግዛት የነበሩ አፍሪካውያን ሀገራቸውን ከአውሮፓውያን ቀጥተኛና የእጅ አዙር ቅኝ አገዛዝ ነጻ ለማውጣትና ህዝባቸውን በተሻለ ማህበራዊ፣ ፖለቲካዊና ምጣኔ ሃብታዊ የዕድገት መንገድ ለመምራት ቅኝ ገዢዎቻቸው ምዕራባውያን ፈላስፎችና መሪዎች ካቀረቡላቸው ርዕዮተ ዓለም የተለየና በአፍሪካውያን ነባር ማህበረሰባዊ ፍልስፍና ላይ የተመሰረተ የራሳቸው የሆነ የፖለቲካ ርዕዮተ ዓለም ፍልስፍና ይዘው በቀረቡ  ልዩ ልዩ የአፍሪካ መሪዎች የሚሰራ ፍልስፍና ነው፡፡ የታንዛንያው የቀድሞ ፕሬዚደንት ጁሊየስ ኔሬሬ የገጠር ሶሻሊዝም ፍልስፍና (Ujamaa)፣ የጋናው ክዋሜ ንክሩማ አፍሪካን አንድ የማድረግ ፍልስፍና (Pan-Africanism)፣ የደቡብ አፍሪካው ታቦ ምቤኪ የአፍሪካ ህዳሴ (African Renaissance) እንዲሁም የቀድሞው የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚንስቴር መለስ ዜናዊ የኢትዮጰያ ህዳሴ (Ethiopian Renaissance) ርዕዮተ ዓለም የዚህ ፍልስፍና ማሳያዎች ናቸው፡፡
አራተናውና የመጨረሻው የአፍሪካውን ፍልስፍና ዘውግ ሙያዊ ፍልስፍና      (professional Philosophy) የሚባለው ነው፡፡ ይህ ዘውግ ፍልስፍናን በዩኒቨርስቲ  ውስጥ በማጥናት ልዩ ልዩ ደረጃ ያለው ዲግሪ ያገኙና በተለያየ ሃላፊነት ላይ የሚገኙ ወይም በአፍሪካ ወይም ከአፍሪካ ውጪ በሚገኙ ዩኒቨርስቲዎች ውስጥ ፍልስፍናን በሚስተምሩ አፍሪካውያን የሚቀርቡ ፍልስፍና ሥራዎች ናቸው፡፡ በዚህ ረገድ የነ ፕሮፌሰር መሳይ ከበደ፣ ቴዎድሮስ ኪሮስ፣ ጸናይ ሰረቀብርሃን ክዋሴ ዊሬዱና ኦዴራ ኦሩካ ከውጪ እንዲሁም የነዶ/ር ዳኛቸው አሰፋ፣ ወርቅነህ ቀልቤሳ፣ በቀለ ጉተማ፣  ጠና ዳዎ ስራዎች ከሀገር ውስጥ የሚጠቀሱ ናቸው፡፡
እንደ ካናዳዊው ኢትዮጵያዊ ክላውድ ሰምነር ማሳመኛ በአቀራረቡም ሆነ በይዘቱ በአስራ ሰባተኛው ክፍለ ዘመን በአውሮፓ ከነበሩ ፈላስፎች ተርታ የሚሰለፈው የዘርዓ ያዕቆብ ፍልስፍና ሌላው የአፍሪካውን ፍልስፍና ገጽታ ነው፡፡
›››››….‹‹‹‹‹

Saturday, June 9, 2012

ኢትዮጵያ ዳግም ልደት አላት ? Ethiopia Renaissance ?

Ethiopian Renaissance

የኢትዮጵያ ህዳሴ

1.1. Renaissance

Renaissance means, according to Burckhardt, “rebirth” or “revival” (Koenigsberger, 1987). The concept represents a wide range of meanings at different times in different contexts across the world. However, the most common and widely known renaissance is the time in Europe When the Italian artists and sculptors recapture and demonstrate an artistic style of Ancient Romans. As the French historian Jules Michelet and the Swiss Jacob  Burckhardrt pointed out in mid-nineteen century “the reawakening or rebirth of valus of the ancient world became the classical view of the Renaissance” (Koenigsberger, 1987, p. 364). Although the Italian Renaissance of the fourteen and fifteen centuriees boldly marks the European renaissance, it is not the first or the only renaissance movement in world history. The caraolingian, the Harlem, Tibetan and African renaissances are instances of other renaissance movements within Europe and outside Europe.

1.1.1.       The Carolingian Renaissance


The carolingian Renaissance is the first renaisance  of the intelelctual acheivement that had taken place in the seventh and eighth century at the time of the carolingian empire (768-814). The central acheivement of this renaissance movement was the rebirth of the teachings of Latin and of Latin Literature both acclesiastical and secular. The movement was led by the group of scholars at Charlemagne’s court.The renaissance was characterized by the revival of learnig and leters ; and is believed to recapture atleast something of a civilization that was recognized as greatly superior (Koenigsberger, 1987, p. 127).

2.1.2.      The Intellectual Renaissance of the 11th and 12th Century


The intellectual renaissance of the 11th and 12th century is the second renaissance in Europe that is characterized by the revival of liberal arts. It was in this renaissance that many universities have been established through out Europe. The intellectuals have managed the establishment of these higher institutions through the process of recovery and assimilation of works of ancients or of any unfamiliar knowledge. The revival of the liberal arts has been succeeded in this renaissance period. The study of the trivium: grammar, rhetoric, and logic, and the quadrivium: geometry, arithmetic, music and astronomy have been continued in a more organized manner. Different universities socialized in different fields. For instance, while Montpelier University in south France specialized in medicine, Bologna University was dedicated itself to he study of law (Koenigsberger, 1987, p. 199). 
This intellectual movement was not only characterized by the revival and assimilation of anceient European works, rather assimilation of  and non-European systems of knowledge was the foundation stone of university education. For instance, intllectuals of the time assimilated Aristotle’s work on Logic , Arab numerals and Avicenna’s “ Canon of Medicine”  with western thinking and system of knowledge . Furthrmore, the revival of  vernacular literature , building, archetecture, sculupture, wall painting and book illustration continued as  it had been in the Carolingian and Ottonian periods. (Koenigsberger, 1987, p. 202)

2.1.3.      The Italian Renaissance

The Italian Renaissance represents the regeneration of Europe’s classical Roman Roots. In this renaissance of the 14th and 15th century a new concept was added to the appreciation of the world of antiquity (Koenigsberger, 1987).  The renaissance began in northern Italy in the late fourteenth century and culminated in England in the early seventeen century. Its emphasis on humanity: the dignity of man (though not woman) and human potential distinguished the renaissance from previous middle ages which was known for its concern for supernatural entities. In poetry and literature, individual thought and action were prevalent, which depictions of the human form becomes a touchstone of renaissance art. In science and medicine the macrocosm and microcosm of human condition inspired remarkable strides in research and discovery.  The impact of the Italian renaissance is not confined to arts and sculpture, however, it also influences history, religion, architecture, literature and language, music, warfare, commerce; exploration, and travel; science and medicine, education as well as daily life of the public in general (Sider, 2007).  
Just as it was the case in the intellectual renaissance in the 11th and 12th centuries, the Italian renaissance is also characterized by assimilation of others (non-European) cultures. Broton argued that though the classical definition of renaissance celebrate the achievements of European civilization to the exclusion of others (non-European), however, since trade, finance, commodities, patronage, imperial conflict, and exchange with different cultures were all key elements of the period, it cannot be true; for instance, the Gentile and Giovanni Bellin’s painting of saint Mark preaching in Alexandria justifies the fact. (Brotton, p. 28). The Renaissance movement is a period of creativity in almost all aspects of life including, painting, sculpture, architecture, ceramics, textile and metalwork. Although many of these objects have since been destroyed or lost, the change in these artifacts and furniture shapes peoples beliefs and attitudes (Brotton, p. 19).

2.1.4.      The Harlem Renaissance

The Harlem Renaissance refers to a cultural movement in the neighborhood of Harlem in New York City during the 1920’s and 1030’s, when literature, art and music flourished in the black community. It was also a time of creativity, when black people had something to say and others were willing to listen (Rav, 2006). The idea is initiated in response to the    historical fact that African-Americans up to this time in American history were thought much like salve, servant or hired hand. Since African-Americans wanted to redefine themselves and reconstruct their identity as a people, because they want to demonstrate where they come from and where they are going they engage in reviving their art and music. By doing so, they managed to boost up their feeling about themselves and showed how they want others to see them.
The rebirth of Herlemites in the 1920s was demonstrated by artistic activities. The black (negro) culture particularly contributed to Americans jazz and blues art. As Huggins pointed out, originally, the black person was proud of his jazz and blues culture; however, this culture ones become dormant and Harlem become notorious for its violence, crime, and poverty. In other words, Harlem came to be known as ghetto for a relatively long period of time. Thus, the concept Harlem renaissance introduced to represent the moment when the culture once dormant has been reawakened on a vision of high culture of jazz; and the flourishing of Harlem from the status of ghetto to a capital of the black ; a platform from which a new black voice would be heard around the world (Huggins, 2007).

2.1.5.       The Tibetan Renaissance

The Tibetan Renaissance signifies the rebirth of Tibetan religious and cultural life. It is a period in Tibetan history, specifically a period after the vigor of the Tibetan imperium (ca. 650-850) and following the dark time of Tibetan social unrest (ca. 850-950). The Tibetan renaissance had not been an overnight project, it was rather a victory over three centuries esoteric religious thought of Buddhist monks and Yogis throughout much of Asia. The major themes of Tibetan renaissance are first, Tibetans interweave together their fragmented culture by using textual and ritual tools provided by Buddhist religious system, especially the late esoteric, Yoga-based system of Indian Tantric Buddhism. Second, during their cultural reemergence, Tibetans wrestled with the processor     translating enormous amount of materials in to an evolving literary languages. In addition, monastery was founded in 1073 and became the fountainhead of several esoteric practices, most notably one known as the path and fruit system (Davidson, 2005). In general, in the process of the renaissance, Tibetan fashioned events almost without parallel in human history: The composition and codification of the Tibetan canon and the creation of Tibetan institutional religious life.

2.1.6.     African Renaissance

African Renaissance is a concept introduced by the South African president Thabo Mbeki as a key component of his governing philosophy. The idea of renaissance though, emerged earlier when Nelson Mandela address to the Organization of African Unity (OAU) in Tunis in 1994, it is Mbeki who has championed it. Ad Bongamba put it Mbeki’s African Renaissance is an imperative for reconfiguring the human conditions in Africa. In his “I am an African” speech that Mbeki delivered on May 8, 1996 to the constitutional assembly of South Africa, he touched on the themes of the African Renaissance laying the emotional, ideological and political basis for his project (Bongmba, 2006, p. 106).

2.1.7.      Ethiopian Renaissance

Ethiopian Renaissance (HIDASSIE) is an idea which has been emerged in 2008 as a governing philosophy of the current Ethiopian government. It was first introduced by the Ethiopian prime minster Meles Zenawi as a motto to the new Ethiopian Millennium. Since the dawn of the prime minster’s articulation of the Ethiopian Renaissance, almost all Ethiopian public mass media started popularizing the idea. Both the Federal and Regional government offices attempted to make the Ethiopian renaissance the ultimate aim for their plans.  Majority of the government officials at different sectors out spoke that they are committed to achieve the Ethiopian Renaissance; and it became common to listen or read the maxim that Ethiopian should strive to secure the irreversibility of the Ethiopia. Although the phrase “Ethiopian Renaissance” becomes a day-to-day language of almost all civil servants in different sectors, it is hardly conceived with precision. Many people could not neatly articulate whether the concept Ethiopian Renaissance is used in a specific and figurative way or in the same way as we have conceived European Renaissance or other non-European Renaissances.  
Ethiopian Renaissance is a very broad concept with various peculiar features as compared to the renaissances we have discusses earlier. Unlike other renaissance movements, this renaissance is only at ideological level. It is Mbeki’s African renaissance that resembles it; for both of them are known philosophically and not practically. Ethiopian renaissance, however, is an ongoing project aimed at achieving some goal. The philosophical foundation for the Ethiopian Renaissance neither exactly resembles other renaissances nor it is entirely a new concept. It is rather a concept emerged as a result of adapting the conceptual frames of other renaissances along with its new features.
The word “Renaissance”, in the context of he Ethiopian renaissance, is defined as rebirth of revival of earlier values. The word is literally used in the same way as it has been defined in the European renaissance (Koenigsberger, 1987). Nonetheless, unlike the European renaissance which is known for its revival of arts (paintings and sculpture), the Ethiopian Renaissance metaphorically emphasizes on the revival of Ethiopian glorious past in general. The Ethiopian renaissance is therefore the rebirth of all aspects of life including the artistic, economic, technological might. Furthermore, like Mbeki’s African renaissance, the Ethiopian renaissance seeks the emotional, ideological and political revival of the country.
The challenge in the Ethiopian renaissance is not only about whether Ethiopian government succeeds in realizing the renaissance project, but also settling the question whether Ethiopia had a glorious past that can be revitalized. Some people[1] even deny the ontological existence of “Old Ethiopia”, “Ethiopian past” or “Ethiopian glorious past. They argue that there was no time in Ethiopian history when Ethiopian had a glorious past in all its political, economic, artistic or technological values; and therefore, the Ethiopian Renaissance is a mere political jargon invented by the ruling political party as a tool to capture the attention of citizens in view of preserving the political power of its regime. The argument goes, although we accept the possibility of Ethiopian history it is a history of hunger, famine, civil war, backwardness and poverty; but not of magnificence.
There is a clear Ethiopian glorious past. As outlined in the preface of “The Battle of Adawa”: “Africa was not simply a “dark continent” out there to be colonized, nor was it simply a necessary link in the inhuman triangular trade, with slavery at one end. It was — and is — also a land of defiance, victory, and pride. (Getachew, 2005) The victory of Adawa is an instance for the existence of the political wonder of Ethiopia’s in the past. As to find evidences for the existence of building and architectural technology might of Ethiopia in the past, one can simply visit the living evidences of the Axum Obelisks in Axum (Berry, 1991) and the Lalibela Rock-Hewn Churches in Wollo. The economic glory of past Ethiopia is characterized by its trade exchanges with a variety of Asian, European, and Middle Eastern countries. The Ancient Greeks, the Byzantine Empire, Portugal, Russia, and the Holy Lands of Jerusalem and Mecca were all familiar with Ethiopia. As Getachew puts in his book “Ethiopia and the United States”: “The US interest in Ethiopia was based on the knowledge of Ethiopia’s past glory; expected economic opportunities for American businesses from an African ‘El Dorado,’as it was touted by American media of the time; and prospects for researchers.” (Getachew M. , 2009).

 In general, Ethiopian Renaissance is a philosophical movement with a profound historical facts and deeper ideological routes. It is an open ended project that may be achieved in a decade, two, half a century, a century or centuries. Whenever the time could be, its actualization is inevitable for the country ones had its own knowledge and value systems that can be revived, provided that Ethiopians jointly strive to achieve it.

As Ethiopian renaissance is a holistic concept, it also incorporates the revival of our ideological: psychological, moral and aesthetical great past. Ideological, I mean Ethiopian had been proud of their identity and patriotic values it had before its contamination with imperialism, neocolonialism and globalization. Ethiopian had had important moral and aesthetical values that have now been eroded, marginalized or forgotten at all. Corruption and absolute egoism that have been prevalent in our society today, for instance, are manifestations for the decline of our indigenous moral system. Thus, by revitalizing our moral values, we can fight corruption and facilitate the possibility of Ethiopian Economic, political, technological and moral renaissance.

In more precise terms, the Ethiopian Renaissance is a symbolic expression of Ethiopia’s desire to bring itself to the level of “developed” countries. Unlike the European, Harlem and Tibetan renaissances that had directly revived their previous artistic and religious values, the Ethiopian renaissance seeks to recapture its entire mighty in almost all aspects of life. Just as the European Renaissance was characterized by creation, regeneration and assimilation of European and non-European knowledge and values, (Koenigsberger, 1987, p. 202) the Ethiopian Renaissance encompasses revival, reformation and preservation of its past values; assimilation of others (European and Non-European) Scientific and technological values; as well as discoveries and innovations.

In contrast to the Italian renaissance which was initiated and led by artists and scholars, the Ethiopian renaissance is initiated by the government. This is illustrated by the fact that the Ethiopian government had already launched a series of grand plans and projects in view of materializing the Ethiopian renaissance. The Growth and Transformation Plan (GTP) which has been launched in 2010; and the Grand Ethiopian Renaissance Dam Project that is being built on Blue Nile River (Abbay) since April 2011 are instances of the move.

The GTP is a five-year period (2010/11-2014/15) national Plan drafted in 2010 by the Ethiopian Ministry of Finance and Economic Development. The medium term plan has also been prepared as part of the countries long term plan, which of course is an important component of the Ethiopian Renaissance. GTP is designed in line with Ethiopia’s long-term vision: 
to become  a  country  where  democratic  rule,  good-governance and social  justice reigns, upon  the  involvement and  free will of its peoples; and once extricating itself from poverty and becomes a middle-income economy.”
And Ethiopian’s vision in the economic sector:
“to build an economy which has a modern and productive agricultural sector with enhanced technology and an industrial sector that plays a leading role in the economy; to sustain economic development and secure social justice; and, increase per capita income of citizens so that it reaches at the level of those in middle-income countries.”  (The Growth and Transformation Plan, 2010)
The primary aim of the GTP is maintaining at least an average real GDP growth rate of 11% and meet the Millennium Development goals, in addition, it is designed in view of  expanding and ensuring the qualities of education and health services thereby achieving the MDGs in the social sectors, third, it is also believed to establish favorable conditions for sustainable state building through the creation of stable democratic and developmental state; and finally, it aims at ensuring growth and  sustainability by realizing all the above objectives within stable macroeconomic framework.  While agriculture makes up eight percent of the composition to the average GDP, industry counts 10 percent (2010, p. 4). This implies that industrialization or technological transformation is a key element in the GTP in particular and the Ethiopian Renaissance in general. As Mulugeta and Abebe explicated, Ethiopia already paved the way towards technological transformation when it made “building capacity to generate, select, import, develop, disseminate, and apply appropriate technologies, and improving knowledge ” its major objectives for its Science and Technology Policy (Mulugeta, 2006).


[1] Some university scholars in Ethiopia  whom I had interview with while collecting data